1 views
መስፈርት: የስራ መደብ፡ የንብረት ስራ አመራር ባለሙያ I ብዛት፡ 2 የስራ መደብ መታወቂያ ቁጥር፡ 2.2/ው/ል/ኮ-282፤283 ደመወዝ፡ 3,526 ደረጃ፡ VIII ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በማቴሪያል ማኔጅመንት፣ ሰፕላይስ ማኔጅመንት፣ ማኔጅመንት፣ አካውንቲንግ ተዛማጅ መስክ እና 0 ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት የስራ ክፍል፡ የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ማሳሰቢያ፡ 1. የስራ ቦታ፡ አዲስ አበባ 2. የቅጥር ሁኔታ፡ በቋሚነት 3. አድራሻ፡ ኃይሌ ገ/ስላሴ ጎዳና ካፒታል ሆቴል አጠገብ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ግቢ፣ 2ኛ ፎቅ የሰው ሃይል አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 210 4. የፈተና ቀን፡ ወደፊት በውስጥ ማስታወቂያ ይገለጻል። 5. አመልካቾች የተጠየቀውን የትምህርት ማስረጃ፣ ትራንስክሪፕት፣ የስራ ልምድ ዋናውን እና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። 6. ከላይ የተገለጸውን የትምህርት ደረጃ እና የስራ ልምድ በላይ ያላችሁ እና ከፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተፈላጊ ችሎታ ጋር አግባብነት ያለው ከሆነ መወዳደር ትችላላችሁ። 7. የስራ ልምድ ማስረጃችሁ ላይ የአገልግሎት ዘመን ቀን፣ ወርና ዓመተ ምህረት እንዲሁም ሲከፈላችሁ የነበረው ደመወዝ መገለጽ ያለበት ሲሆን ከግል ድርጅቶች የተገኘ የስራ ልምድ የስራ ግብር እና ጡረታ ከደመወዛችሁ ላይ እየተቀነሰ ለሚመለከተው አካል ገቢ መደረጉ መገለጽ አለበት። ለበለጠ መረጃ፡ 011 6 63 65 08 በመደወል መጠየቅ ይቻላል። ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።