1 views
መስፈርት: የስራ መደብ፡ የመጠጥ ውሃ መሃንዲስ I ብዛት፡ 1 የስራ መደብ መታወቂያ ቁጥር፡ 2.2/ው/ል/ኮ-198 ደመወዝ፡ 4,150 ደረጃ፡ IX ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ በሲቪል ምህንድስና ወይም በመጠጥ ውሃ ምህንድስና ወይም በሃይድሮሊክስ ምህንድስና ወይም በውሃ ኃብት ልማት ምህንድስና ወይም በአፈርና ውሃ ምህንድስና እና 0 ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት የስራ ክፍል፡ የአስቸኳይ ጊዜ መ/ው/ሳ/ል/ድ/ ዳይሬክቶሬት ማሳሰቢያ፡ 1. የስራ ቦታ፡ አዲስ አበባ 2. የቅጥር ሁኔታ፡ በቋሚነት 3. አድራሻ፡ ኃይሌ ገ/ስላሴ ጎዳና ካፒታል ሆቴል አጠገብ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ግቢ፣ 2ኛ ፎቅ የሰው ሃይል አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 210 4. የፈተና ቀን፡ ወደፊት በውስጥ ማስታወቂያ ይገለጻል። 5. አመልካቾች የተጠየቀውን የትምህርት ማስረጃ፣ ትራንስክሪፕት፣ የስራ ልምድ ዋናውን እና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። 6. ከላይ የተገለጸውን የትምህርት ደረጃ እና የስራ ልምድ በላይ ያላችሁ እና ከፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተፈላጊ ችሎታ ጋር አግባብነት ያለው ከሆነ መወዳደር ትችላላችሁ። 7. የስራ ልምድ ማስረጃችሁ ላይ የአገልግሎት ዘመን ቀን፣ ወርና ዓመተ ምህረት እንዲሁም ሲከፈላችሁ የነበረው ደመወዝ መገለጽ ያለበት ሲሆን ከግል ድርጅቶች የተገኘ የስራ ልምድ የስራ ግብር እና ጡረታ ከደመወዛችሁ ላይ እየተቀነሰ ለሚመለከተው አካል ገቢ መደረጉ መገለጽ አለበት። ለበለጠ መረጃ፡ 011 6 63 65 08 በመደወል መጠየቅ ይቻላል። ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።