1 views
የኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለስልጣን ከዚህ በታች በተጠቀሰው ክፍት የስራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል። የስራ መደቡ መጠሪያ፡ ኤክስኪዩቲቭ ሴክሬታሪ I ደመወዝ፡ 4,150.00 ብዛት፡ 1 ተፈላጊ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ፡ የጽህፈትና ቢሮ አስተዳደር/በሴክሬተሪያል ሳይንስና ኦፊስ ማኔጅመንት ዲፕሎማ ወይም የቴክኒክና ሙያ በደረጃ 3 የማረጋገጫ /10+3/ ያለው/ያላት እና 4 ዓመት የስራ ልምድ (COC) ማቅረብ የሚችል። የስራ ቦታ፡ አዲስ አበባ ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርትና ከዚያ በላይ የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃዎቻችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ በባለስልጣኑ የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 24 በመቅረብ አስፈላጊውን ማስረጃና ሲቪ በመያዝ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። - ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ። - በሌብል ለተመረቁ COC ያስፈልጋል። ለበለጠ መረጃ፡ ስልክ ቁጥር፡ 011 550 77 33/35 ባልቻ ሆስፒታል ጀርባ ሳጂዳ ቢዝነስ ሴንተር 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 24