ብሔራዊ የቆላ ዝንብና ገንዲ በሽታ መቆጣጠሪያና ማጥፊያ ኢንስቲትዩት ከዚህ በታች በተጠቀሰው ክፍት የስራ መደብ ላይ መስፈርቱን የሚያሟሉ ሰራተኞችን በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል። የስራ መደቡ መጠሪያ፡ ራዲየሽን ኦፕሬተር ደመወዝ፡ 2,344 ብዛት፡ 1 የትምህርት ደረጃ፡ የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ዓይነት፡ በፊዚክስ፣ በኬሚስትሪ፣ በራዲዮሎጂ፣ በኤሌክትሪሲቲ ወይም በኤሌክትሮኒክስ ኢንጅነሪንግ የስራ ልምድ፡ 0 ዓመት የስራ ቦታ፡ ቃሊቲ ማዕከል /አዲስ አበባ/ ማሳሰቢያ፡ - የቅጥር ሁኔታ፡ በቋሚነት - ከዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ በላይ ያላቸው ተወዳዳሪዎች ማመልከት ይችላሉ። - በሌቭልና በዲፕሎማ የምታመለክቱ ተወዳደሪዎች የብቃት ማረጋገጫ (COC) ማቅረብ ይኖርባችኋል። - የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ወደፊት ይገልጻል። - አመልካቾች ለምዝገባ በሚመጡበት ሰዓት ኦሪጅናልና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባችኋል። - ከግል ተቋማት የሚቀርቡ የስራ ልምድ ግብር የተከፈለበት መሆን አለበት። የመመዝገቢያ ቦታ እና ለተጨማሪ መረጃ፡ - ብሔራዊ የቆላ ዝንብና ገንዲ በሽታ መቆጣጠሪያና ማጥፊያ ኢንስቲትዩት፡ ልዩ ቦታ ቃሊቲ ገብርኤል ከ40/60 ኮንዶሚኒየም ጀርባ የሰው ሃብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 05 ስልክ ቁጥር፡ 011 4 39 62 82